በግንቦት ወር 2017 አም የአቦርጅናል እና ቶረስ ስትሬት አይላንደር ተወካዮች በአንድ ላይ በመሆን በመጀመሪያው ብሄራዊ ህገ መንግስት ስምምነት ዙሪያ በኡሉሩ አቅራቢያ ተሰባስበን የኡሉሩን መግለጫ ከልባችን በማፍለቅ ለአውስትራሊያ ህዝብ አቅርበናል። መግለጫው የመጀመሪያዎቹ ዜጎች በህገ-መንስቱ እንዲካተት ለፓርላምው ድምጻቸው ያሰሙበት ፤ እንዲሁም እውነትን በመናገር ላይ የተመሰረተ ስምምነት (ውል ) ላይ ለመደረስ ይመሩበት ሂደት ነው ። ይህ ከአውስትራሊያ ቀደምት ዜጎች ጋር በአገር አቀፍ ደረጃ በየክልሉ ተደርገው ከነብሩት 13 ውይይቶች ማጠቃለያ የተገኘ ውጤት ነው ። መግለጫውም በአውስትራሊያ ቀደምት ዜጎች እና የአውስትራሊ ዜጎች ማካከል በእውነት ፤ በፍትህ እና የራስን መብት በራስ መወሰን ላይ ላይ የተመሰረተ ግንኙነትን ለመመስረት የሚሻ ነው ። ሙዚቃ ፍራንክ ያማ ፤ፎቶግራፍ ፡ ጂሚ ዊደርስ ሃንት ።